ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያ (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሰውየው የሚያገኘው ያሰበውን ነው። ስደ...
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሁሉም ስራዎች ግምት የሚሰጣቸው በኒያ እንደሆነ አብራሩ። ይህ ብይን በአምልኳዊም ጉዳይ ሆነ ከሰው ጋር ባሉ መስተጋብሮች ሁሉንም ስራዎች የሚያጠቃልል ነው። በስራው የሆነን ጥቅም ያሰበ ሰው ከዛች ጥቅም በስተቀ...
ከእናታችን ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ ብላለች: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: ‹በዚህ በመመሪያችን ውስጥ ከርሱ (ከትእ...
በሃይማኖት ውስጥ አዲስ ነገር የፈጠረ ወይም ቁርአናዊና ሐዲሣዊ ማስረጃ ያልጠቆሙትን ስራ የሰራ ሰው በባለቤቱ ላይ ተመላሽ እንደሚሆንና አላህ ዘንድም ተቀባይነት እንደማይኖረው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ።
ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ ከዕለታት አንድ ቀን የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘንድ ሳለን ድንገት ልብሱ እጅግ በጣም ነጭ የሆነ፤ ፀጉሩ ደግሞ እጅግ በጣም ጥቁር...
ዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ከዕለታት አንድ ቀን ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም በሶሐቦች መካከል አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና በማይታወቅ ሰው ተመስሎ እንደወጣ ይናገራሉ። ከዚህም ሰውዬ ባህሪ ልብሱ እጅግ...
ከዐብደላህ ቢን ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: «እስልምና በአምስት መሰረቶች ተገነ...
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ኢስላምን አምስት አስተማማኝ ምሶሶዎች እንደተሸከሙት ቤት አድርገው መሰሉት። የተቀሩትን የኢስላም ጉዳዮች ደግሞ ቤቱን እንደሚያሟሉ ነገሮች ናቸው። ከእነዚህ ማእዘናት የመጀመሪያው: ሁ...
ሙዓዝ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ : ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ኋላ ዑፈይር የሚባለው አህያ ላይ ተፈናጥጬ ሳለው "ሙዓዝ ሆይ አላህ በባሮቹ ላይ ያለውን ሐቅ፤ ባሮችስ አላህ ዘንድ ያላቸ...
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አላህ በባሮቹ ላይ ያለውን ሐቅና ባሮች አላህ ዘንድ ያላቸውን ሐቅ አብራሩ። አላህ ባሮቹ ላይ ያለው ሐቅ እሱን ብቻ ሊያመልኩና በሱ ላይ አንዳችንም ላያጋሩ ነው። ባሮች በአላህ ላይ ያላቸ...

ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያ (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሰውየው የሚያገኘው ያሰበውን ነው። ስደቱ ወደ አላህና መልክተኛው የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳም) ወደ አላህና መልክተኛው ነው። ስደቱ ለዱንያ ጥቅማጥቅም ለማግኘት ወይም ሴትን ለማግባት የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳ) ወደ ተሰደደበት ነገር ወደዛው ነው።" በቡኻሪ ዘገባ ደግሞ፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።"

ከእናታችን ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ ብላለች: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: ‹በዚህ በመመሪያችን ውስጥ ከርሱ (ከትእዛዛችን) የሌለን አዲስ ነገር የፈጠረ ሰው እርሱ (የፈጠረው አዲስ ነገር) ተመላሽ ነው።›" ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል። በሙስሊም ዘገባ "ትእዛዛችን የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው እርሱ (ሥራው) ተመላሽ ነው።"

ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ ከዕለታት አንድ ቀን የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘንድ ሳለን ድንገት ልብሱ እጅግ በጣም ነጭ የሆነ፤ ፀጉሩ ደግሞ እጅግ በጣም ጥቁር የሆነ ሰውዬ ብቅ አለ። በሱ ላይ የጉዞ ምልክት አይታይበትም፤ ከኛ ውስጥም አንድም የሚያውቀው ሰው የለም፤ ወደ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘንድ መጥቶ ተቀመጠ። ጉልበቱን ወደ ጉልበታቸው አስጠጋ፤ መዳፎቹንም በታፋዎቹ ላይ አደረገና "ሙሐመድ ሆይ! ስለ ኢስላም ንገረኝ!" አላቸው። የአላህ መልዕክተኛም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ኢስላም ማለት ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን ልትመሰክር፣ ሰላት ደንብና ስርዓቱን ጠብቀህ ልትሰግድ፣ ዘካን ልትሰጥ ፣ ረመዷንን ልትፆምና ወደርሱ መንገድን ከቻልክም የአላህን ቤት ልትጎበኝ ሐጅ ልታደርግ ነው።" አሉት። እሱም "እውነት አልክ!" አላቸው። "በሱ ተገረምን ይጠይቃቸዋልም (ጥያቄውን በትክክል እንደመለሱ) ያረጋግጥላቸዋልም።" ከዚያም፦ "ስለኢማን ንገሩኝ!" አላቸው። እሳቸውም "በአላህ፣ በመላእክቱ፣ በመጻሕፍቱ፣ በመልክተኞቹ፣ በመጨረሻው ቀንና በጥሩውም ሆነ መጥፎ ውሳኔዎቹም ልታምን ነው።" አሉት። እሱም "እውነት አልክ!" አላቸው። "ስለኢሕሳን (በጎ መስራት) ንገሩኝ!" አላቸው። እሳቸውም "አላህን ልክ እንደምታየው ሆነህ ልትገዛው ነው። አንተ ባታየው እንኳ እርሱ ያይሀልና።" አሉት። "ስለ ሰዓቱቱ (ቂያማ) ንገረኝ!" አላቸው። እሳቸውም "ስለርሷ ተጠያቂው ከጠያቂው የበለጠ አዋቂ አይደለም።" አሉት። "ስለ ምልክቶቿ ይንገሩኝ!" አለ። እሳቸውም "ባሪያ ጌታዋን ልትወልድ ነው ፤ ያልተጫማ፣ የታረዘ፣ ድሃና የፍየል እረኛ የሆኑ ሰዎች ለህንፃዎች ሲሽቀዳደሙ ማየትህ ነው።" አሉት። ዑመር እንዲህ አለ "ከዚያም ሄደ። የተወሰነ ጊዜ ቆየሁ። ከዚያም ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ዑመር ሆይ! ጠያቂው ማን እንደነበር አውቀሀልን?" አሉኝ። እኔም "አላህና መልክተኛው ያውቃሉ።" አልኳቸው። እሳቸውም "እርሱ ጂብሪል ነው እምነታችሁን ሊያሳውቃችሁ መጥቷችሁ ነው።" አሉ።

ከዐብደላህ ቢን ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: «እስልምና በአምስት መሰረቶች ተገነባ እነርሱም: 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወአንነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ' (ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም፤ ሙሐመድም የአላህ ባሪያና መልክተኛ ናቸው።) ብሎ መመስከር፣ ሶላትን ማቋቋም፣ ዘካ መስጠት፣ በተከበረው የአሏህ ቤት ሐጅ ማድረግ እና የረመዷንን ወር መፆም ናቸው።'»

ሙዓዝ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ : ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ኋላ ዑፈይር የሚባለው አህያ ላይ ተፈናጥጬ ሳለው "ሙዓዝ ሆይ አላህ በባሮቹ ላይ ያለውን ሐቅ፤ ባሮችስ አላህ ዘንድ ያላቸውን ሐቅ ታውቃለህን? " አሉ። "አላህና መልክተኛው ይወቁ !" አልኩኝ። እሳቸውም "አላህ በባሮቹ ላይ ያለው ሐቅ ሊገዙትና በሱ ላይም አንዳችንም ላያጋሩ ሲሆን፤ ባሮች በአላህ ዘንድ ያላቸው ሐቅ ደግሞ በሱ ላይ አንዳችንም ያላጋራን ላይቀጣ ነው።" አሉ። "የአላህ መልክተኛ ሆይ ይህን ሰዎችን ላበስራቸውን?" አልኳቸው። እሳቸውም "አታበስራቸው (በዚህ ስራ ብቻ) ይደገፋሉ (ይሳነፋሉ)። " አሉ።

ከአነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና- እንደተላለፈው: "ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ግመል ላይ ሆነው ሙዓዝ ከኃላ ተፈናጦ ሳለ እንዲህ አሉ: 'አንተ ሙዓዝ ቢን ጀበል ሆይ' እርሱም ሶስቴ 'አቤት ብያለው በደስታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!' አሁንም 'ሙዓዝ ሆይ!' አሉት: እሱም 'አቤት ብያለው በደስታ የአላህ መልክተኛ ሆይ!' አለ። ሶስት ጊዜ ደገሙትና ቀጥለውም ' አላህ በእርሱ ላይ እሳትን እርም ቢያደርግ እንጂ አንድም በእውነተኛ ልቡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን የሚመሰክር የለም።' አሉ። እርሱም 'የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህንን ለሰዎች ነገሬ ላበስራቸው እንዴ?' አለ። እሳቸውም 'ከነገርካቸውማ (በዚህ ሐዲሥ ላይ) ይደገፋሉ (ይሰንፋሉ)።' አሉ። ሙዓዝ ይህንን ሐዲስ የተናገረው ወንጀል ውስጥ ላለ መውደቅ ብሎ ሊሞት ሲል ነው።"

ከጧሪቅ ቢን አሽየም አልአሽጀዒይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ለዋሏል: "የአላህን መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ: 'ላኢላሃ ኢለሏህ ብሎ ከአላህ ውጪ በሚመለኩ ነገሮች የካደ ሰው ገንዘቡም ደሙም እርም ይሆናል። ሂሳቡ ያለው አላህ ላይ ነው።'"

ጃቢር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፦ ወደ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ዘንድ አንድ ሰውዬ በመምጣት እንዲህ አለ፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ሁለቱ (ጀነትና እሳትን) የሚያስወስኑ ነገሮች ምንድናቸው?" እሳቸውም "በአላህ ላይ አንዳችንም ሳያጋራ የሞተ ሰው ጀነት ገባ፤ በአላህ ላይ አንዳችን እያጋራ የሞተ ሰው እሳት ገባ።" አሉ።

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንዷን ተናገሩ እኔ ደግሞ ሌላዋን ተናገርኩ። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: ‹ ከአላህ ውጪ ሌላን ቢጤን (ባላንጣን) እየተጣራ የሞተ ሰው እሳት ገባ።› እኔ ደግሞ: ‹ለአላህ ሌላን ቢጤን (ባላንጣን) ሳይጣራ የሞተ ሰው ጀነት ይገባል።› አልኩኝ።"

ከኢብኑ ዐባስ ረዲየሏሁ ዐንሁማ እንደተላለፈው እንዲህ ብሏል፡ "የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሙዐዝ ቢን ጀበልን ወደ የመን በሚልኩበት ጊዜ እንዲህ አሉት፡ ' አንተ የመጽሐፍ ባለቤት ወደሆኑ ህዝቦች ትሄዳለህ። ስለዚህም እነርሱ ዘንድ ስትደርስ ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና ሙሐመድም የአሏህ መልዕክተኛ መሆናቸውን ወደ መመስከር ጥሪ አድርግላቸው። እነሱ ለዚህ ጥሪህ ታዛዥ ከሆኑ አሏህ በነሱ ላይ በቀንና ምሽቱ ሁሉ አምስት ሶላቶችን ግዴታ እንዳደረገባቸው አሳውቃቸው። ለዚህ ጥሪህም ታዛዥ ከሆኑ አላህ በነሱ ላይ ከሀብታሞቻቸው ተይዞ ወደ ድሆቻቸው የምትሰጥ ምፅዋት ግዴታ እንዳደረገባቸው አሳውቃቸው። ለዚህ ጥሪህም ታዛዦች ከሆኑ አደራህን ውድ የሆኑ ንብረቶቻቸውን (ገንዘቦቻቸውን) ተጠንቀቅ! የተበዳይንም ልመና ተጠንቀቅ! እነሆ በሷና በአላህ መሀል ግርዶሽ የለምና።'"

አቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ማለታቸው ተላልፏል፡ "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! የቂያማ ቀን በርሶ ምልጃ ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛው ማን ነው?" ተባሉ። የአላህ መልዕክተኛም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ አሉ፡- 'አቡ ሁረይራ ሆይ! ባንተ ላይ ካየሁት የሐዲሥ ጉጉት አንፃር ይህንን ጥያቄ ለመጠየቅ የሚቀድምህ አይኖርም ብዬ አስቤ ነበር። የቂያማ ቀን በኔ አማላጅነት ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛ የሚሆኑት ጥርት ባለ መልኩ ከልባቸው ወይም ከነፍሳቸው 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ያሉት ናቸው።'"

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: "የአላህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወስለም እንዲህ ብለዋል: 'ኢማን ሰባ ምናምን ወይም ስልሳ ምናምን ክፍሎች አሉት። በላጩ ክፍልም 'ላኢላሃ ኢለሏህ' ማለት ሲሆን ዝቅተኛው ክፍል መጥፎን ነገር ከመንገድ ላይ ማስወገድ ነው። ሓያእ (አይነ አፋርነትም) የኢማን አንዱ ክፍል ነው።'"