ዋና ገፅ
እኛ ማን ነን
am
English
العربية
español
português
Français
Русский
اردو
azərbaycanca
Ўзбек
Deutsch
Shqip
فلبيني مرناو
براهوئي
български
বাংলা
ဗမာ
bosanski
polski
தமிழ்
ไทย
татар теле
română
isiZulu
سنڌي
සිංහල
Kiswahili
svenska
нохчийн мотт
Soomaali
тоҷикӣ
غجري
Pulaar
Pulaar
Tiếng Việt
قمري
कश्मीरी
한국어
македонски
bahasa Melayu
മലയാളം
magyar
हिन्दी
Hausa
Èdè Yorùbá
ελληνικά
қазақ тілі
فارسی
Türkçe
עברית
中文
Bahasa Indonesia
Wikang Tagalog
dansk
پښتو
Tamazight
አማርኛ
أنكو
ئۇيغۇرچە
Luganda
తెలుగు
日本語
ትግርኛ
غموقي
Кыргызча
नेपाली
Kurdî
italiano
Nederlands
čeština
українська
eesti
suomi
Адыгэбзэ
Norwegian
latviešu
slovenščina
монгол
íslenska
ქართული
tamashaq
ދިވެހި
Հայերէն
slovenčina
Afrikaans
Türkmençe
башҡорт теле
afaan oromoo
ភាសាខ្មែរ
ಕನ್ನಡ
Bassa
Lingala
lietuvių
bamanankan
Soninke
Malagasy
Mandinka
Sängö
Wollof
Cham
Qhichwa simi
Српски
Afaraf
hrvatski
Kinyarwanda
aymar aru
Jóola
Bi zimanê Kurdî
Akan
ଓଡ଼ିଆ
Chichewa
авар мацӀ
Igbo
isiXhosa
मराठी
Fɔ̀ngbè
ગુજરાતી
Mɛnde
ГӀалгӀай
Mõõré
অসমীয়া
Maguindanao
Dagbani
Yao
Ikirundi
Bisaya
Ruáingga
فارسی دری
Sesotho
ਪੰਜਾਬੀ
créole
ພາສາລາວ
ዋና ገፅ
እኛ ማን ነን
Contact Us
/
ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።
ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።
ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያ (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሰውየው የሚያገኘው ያሰበውን ነው። ስደቱ ወደ አላህና መልክተኛው የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳም) ወደ አላህና መልክተኛው ነው። ስደቱ ለዱንያ ጥቅማጥቅም ለማግኘት ወይም ሴትን ለማግባት የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳ) ወደ ተሰደደበት ነገር ወደዛው ነው።" በቡኻሪ ዘገባ ደግሞ፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።"
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
ትንታኔ
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሁሉም ስራዎች ግምት የሚሰጣቸው በኒያ እንደሆነ አብራሩ። ይህ ብይን በአምልኳዊም ጉዳይ ሆነ ከሰው ጋር ባሉ መስተጋብሮች ሁሉንም ስራዎች የሚያጠቃልል ነው። በስራው የሆነን ጥቅም ያሰበ ሰው ከዛች ጥቅም በስተቀር ሌላ አያገኝም። ምንዳም የለውም። በስራው ወደ አላህ መቃረብን ያሰበ ሰው ደግሞ እንደ መብላትና መጠጣት የመሰሉ ተለምዷዊ ስራ ቢሆንም እንኳ ሰርቶ በስራው ምንዳና አጅርን ያገኛል። ቀጥለውም ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስራዎች በውጫዊ ይዘታቸው ሲታዩ ተመሳሳይ ከመሆናቸውም ጋር ኒያ በስራዎች ላይ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ለማብራራት ምሳሌ ጠቀሱ። በስደቱና ሀገሩን በመተዉ የአላህን ውዴታ ማግኘትን ያሰበ ስደቱ ሸሪዐዊና ተቀባይነት ያለው ስደት ነው። ኒያው እውነተኛ ስለሆነም ይመነዳበታል። በስደቱ ግን እንደ ገንዘብ፣ ክብር፣ ንግድና ሚስት የመሳሰሉ ዓለማዊ ጥቅም የፈለገ ሰው ከስደቱ ይህችን ያሰባትን ጥቅም በስተቀር ሌላ አያገኝም። ከምንዳና አጅርም ምንም እጣ ፈንታ እንደሌለው ገለፁ።
Hadeeth benefits
በኢኽላስ ላይ መበረታታቱ ፤ አላህ የሱ ፊት ተፈልጎበት የተሰራን ስራ ካልሆነ በስተቀር ምንም ስራ አይቀበልምና።
አንድ ሸሪዓዊ ብይኖች የሚመለከቱት ዕድሜ ክልል ላይ የደረሰ ሰው ወደ አላህ የሚቃረብበትን ስራ በተለምዷዊ እሳቤ ቢሰራው በስራው ወደ አላህ መቃረብን እስኪያስብ ድረስ በሷ አማካኝነት ምንም ምንዳ አይኖረውም።
Share
Use the QR code to easily share the message of Islam with others
Copy Link
copied!
ተገናኘን
×
ስም
ኢሜይል
የጽሑፉ መልዕክት
ተገናኘን
×
መልክት በመላኪህ እናመሰግናለን ...አላህ ካለ እናየዋለን
Share