/ 'ንገሩኝ እስኪ! አንዳችሁ በር ላይ በየቀኑ አምስት ጊዜ የሚታጠብበት ወንዝ ቢኖር ይህ ከእድፉ ያስቀራል ትላላችሁን?

'ንገሩኝ እስኪ! አንዳችሁ በር ላይ በየቀኑ አምስት ጊዜ የሚታጠብበት ወንዝ ቢኖር ይህ ከእድፉ ያስቀራል ትላላችሁን?

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህን መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ አሉ፦ "'ንገሩኝ እስኪ! አንዳችሁ በር ላይ በየቀኑ አምስት ጊዜ የሚታጠብበት ወንዝ ቢኖር ይህ ከእድፉ ያስቀራል ትላላችሁን?' ሶሐቦችም 'ከእድፉ አንዳችም አያስቀርም።' አሉ። እርሳቸውም 'ይህ የአምስቱ ሶላቶች ምሳሌ ነው። አላህ በሶላት ወንጀሎችን ያብሳል።' አሉ።"
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በጧትም በማታም የሚሰገዱትን አምስቱ ሶላቶች ትናንሽ ወንጀሎችንና ኃጢአቶችን ማስማራቸውና ማስወገዳቸውን፤ አንድ ሰው በየቀኑ አምስት ጊዜ የሚታጠብበት በሆነ በሩ ላይ እንዳለ ወንዝ መሰሉት። ከእድፉና ቆሻሻው አንዳችም አይቀርምና።

Hadeeth benefits

  1. ይህ ትሩፋት ትናንሽ ወንጀሎችን ብቻ በማስማር የተገደበ ነው። ትላልቅ ወንጀሎች የግድ ተውበት ያስፈልጋቸዋል።
  2. አምስቱን ሶላቶች የመፈፀምና የእነርሱን መስፈርቶች፣ ማእዘናቶች፣ ግዴታዎችና ሱናዎችን የመጠባበቅን ትሩፋት እንረዳለን።