/ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት የወጡ ጊዜ "ጉፍራነክ" ይሉ ነበር።» (ትርጉሙም "ምህረትህን እለምንሃለሁ" ማለት ነው።)...

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት የወጡ ጊዜ "ጉፍራነክ" ይሉ ነበር።» (ትርጉሙም "ምህረትህን እለምንሃለሁ" ማለት ነው።)...

የአማኞች እናት ከሆነችው ከዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው፦ «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት የወጡ ጊዜ "ጉፍራነክ" ይሉ ነበር።» (ትርጉሙም "ምህረትህን እለምንሃለሁ" ማለት ነው።)
አቡዳውድ፣ ቲርሚዚ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከመፀዳጃ ቤት ተፀዳድተው ሲወጡ አላህ ሆይ ምህረትህን እጠይቃለሁ ይሉ ነበር።

Hadeeth benefits

  1. ከመፀዳጃ ስፍራ ሲወጣ "ጉፍራነክ" ማለት እንደሚወደድ እንረዳለን።
  2. ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሁሉም ሁኔታቸው ጌታቸውን ምህረት እንደሚጠይቁ እንረዳለን።
  3. ከመፀዳጃ ቤት ሲወጣ ምህረትን የሚጠየቅበት ምክንያት አላህን ለብዙ ፀጋዎቹ ከማመስገን ስላጓደልን ሲሆን ከነዛም ፀጋዎቹ መካከል የሚያውከንን ነገር እንዲወጣ ማቅለሉ አንዱ ነው። በምፀዳዳበት ወቅት አንተን ከማውሳት ስለተጠመድኩ ምህረትህን እጠይቅሃለሁ ይባላልም ብለዋል።