ዋና ገፅ
እኛ ማን ነን
am
English
العربية
español
português
Français
Русский
اردو
azərbaycanca
Ўзбек
Deutsch
Shqip
فلبيني مرناو
براهوئي
български
বাংলা
ဗမာ
bosanski
polski
தமிழ்
ไทย
татар теле
română
isiZulu
سنڌي
සිංහල
Kiswahili
svenska
нохчийн мотт
Soomaali
тоҷикӣ
غجري
Pulaar
Pulaar
Tiếng Việt
قمري
कश्मीरी
한국어
македонски
bahasa Melayu
മലയാളം
magyar
हिन्दी
Hausa
Èdè Yorùbá
ελληνικά
қазақ тілі
فارسی
Türkçe
עברית
中文
Bahasa Indonesia
Wikang Tagalog
dansk
پښتو
Tamazight
አማርኛ
أنكو
ئۇيغۇرچە
Luganda
తెలుగు
日本語
ትግርኛ
غموقي
Кыргызча
नेपाली
Kurdî
italiano
Nederlands
čeština
українська
eesti
suomi
Адыгэбзэ
Norwegian
latviešu
slovenščina
монгол
íslenska
ქართული
tamashaq
ދިވެހި
Հայերէն
slovenčina
Afrikaans
Türkmençe
башҡорт теле
afaan oromoo
ភាសាខ្មែរ
ಕನ್ನಡ
Bassa
Lingala
lietuvių
bamanankan
Soninke
Malagasy
Mandinka
Sängö
Wollof
Cham
Qhichwa simi
Српски
Afaraf
hrvatski
Kinyarwanda
aymar aru
Jóola
Bi zimanê Kurdî
Akan
ଓଡ଼ିଆ
Chichewa
авар мацӀ
Igbo
isiXhosa
मराठी
Fɔ̀ngbè
ગુજરાતી
Mɛnde
ГӀалгӀай
Mõõré
অসমীয়া
Maguindanao
Dagbani
Yao
Ikirundi
Bisaya
Ruáingga
فارسی دری
Sesotho
ਪੰਜਾਬੀ
créole
ພາສາລາວ
ዋና ገፅ
እኛ ማን ነን
Contact Us
/
ሞት በቡራቡሬ ሙክት ተመስሎ ተይዞ ይመጣል
ሞት በቡራቡሬ ሙክት ተመስሎ ተይዞ ይመጣል
አቡ ሰዒድ አልኹድሪይ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፦ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "ሞት በቡራቡሬ ሙክት ተመስሎ ተይዞ ይመጣል። ተጣሪም እንዲህ በማለት ይጣራል: "የጀነት ባለቤቶች ሆይ!" ተንጠራርተው ይመለከታሉ። "ይህንን ታውቁታላችሁን?" ይላቸዋል። "አዎን ይህ ሞት ነው ሁሉም ተመልክቶታል።" ይላሉ። ቀጥሎ ተጣሪው እንዲህ በማለት ይጣራል "የእሳት ባለቤቶች ሆይ!" ተንጠራርተው ይመለከታሉ። "ይህንን ታውቁታላችሁን?" ይላቸዋል። "አዎን ይህ ሞት ነው ሁሉም ተመልክቶታል።" ይላሉ። ይታረዳል ቀጥሎ እንዲህ ይላቸዋል "የጀነት ባለቤቶች ሆይ! (ከዚህ በኋላ) ዘላለማዊ ሕይወት እንጂ ሞት የለባችሁም። የእሳት ባለቤቶች ሆይ! (ከዚህ በኋላ) ዘላለማዊ ሕይወት እንጂ ሞት የለባችሁም።" ከዚያም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን፦ {እነሱም (አሁን) በዝንጋቴ ላይ ሆነው ሳሉ ነገሩ በሚፈረድበት ጊዜ የቁጭቱን ቀን አስፈራራቸው።} [መርየም: 39] የሚለውን አንቀፅ አነበቡ። "እነዚህ በዱንያ ዝንጋቴ ውስጥ ናቸው።" {እነሱም የማያምኑ ናቸው።} [መርየም: 39]"
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
ትንታኔ
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የትንሳኤ ቀን ሞት ጥቁርና ነጭ በሆነ ወንድ በግ ተመስሎ ተይዞ እንደሚመጣ አብራሩ። "የጀነት ባለቤቶች ሆይ!" ተብሎ ይጠራል። አንገቶቻቸውንና ትከሻዎቻቸውን በመለጠጥ ጭንቅላታቸውንም በማንጠራራት ይመለከታሉ። ለነሱም "ይህንን ታውቁታላችሁን?" ይላቸዋል። እነሱም "አዎን ይህ ሞት ነው። ሁሉም አይቶታል ያውቀዋል።" ይላሉ። ከዚያም ተጣሪው "የእሳት ባለቤቶች ሆይ!" በማለት ይለፍፋል። አንገቶቻቸውንና ትከሻዎቻቸውን በመለጠጥ ጭንቅላታቸውንም በማንጠራራት ይመለከታሉ። ለነሱም "ይህንን ታውቁታላችሁን?" ይላቸዋል። እነሱም "አዎን ይህ ሞት ነው። ሁሉም አይቶታል።" ይላሉ። ሙክቱ ይታረዳል ከዚያም ተጣሪው፦ "የጀነት ባለቤቶች ሆይ! እጣፈንታችሁ ያለሞት ዘውትርና ዘላለም መኖር ነው። የእሳት ባለቤቶች ሆይ! እጣፈንታችሁ ያለሞት ዘውትርና ዘላለም መኖር ነው።" ይላቸዋል። ይህም ለአማኞች ተጨማሪ ፀጋ ለከሀዲያን የቅጣት አለንጋ እንዲሆን ነው። ከዚያም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ይህን አንቀፅ አነበቡ። {እነሱም (አሁን) በዝንጋቴ ላይ ሆነው ሳሉ እነሱም የማያምኑ ሲኾኑ ነገሩ በሚፈረድበት ጊዜ የቁጭቱን ቀን አስፈራራቸው።} [መርየም: 39] የትንሳኤ ቀን በጀነትና እሳት ባለቤቶች መሀል ይፈረዳል። ሁሉም ወደሚዘወትርባት ይገባል። ወንጀለኛ በጎ ባለመሥራቱ ይፀፀታልም ይቆጫልም። መልካም ከመስራት ያጓደለም ባለመጨመሩ ይቆጫል።
Hadeeth benefits
የሰው ልጅ በመጪው ዓለም መመለሻው ጀነት ውስጥ ወይም እሳት ውስጥ መዘውተር ነው።
ስለ ትንሳኤ ቀን መከራ ከባድ ማስፈራሪያ መምጣቱ። እሱ የቁጭትና ፀፀት ቀን ነው።
የጀነት ባለቤቶች ደስታ እንደሚዘወትር፤ የእሳት ባለቤቶች ሀዘንም እንደሚዘወትር መገለፁ።
Share
Use the QR code to easily share the message of Islam with others
Copy Link
copied!
ተገናኘን
×
ስም
ኢሜይል
የጽሑፉ መልዕክት
ተገናኘን
×
መልክት በመላኪህ እናመሰግናለን ...አላህ ካለ እናየዋለን
Share