- ሰሑር መብላትና ሸሪዓዊ ትእዛዝን ተግባራዊ ማድረግ ይወደዳል።
- ኢብኑ ሐጀር በፈትሑል ባሪይ ውስጥ እንዲህ ብለዋል: "በሰሑር የሚገኘው በረከት በበርካታ መንገዶች ይገኛል። ሰሑር መብላት ሱናን መከተል ነው፤ የመጽሐፉ ሰዎችን መቃረን ነው፤ ለአምልኮ ማጠናከሪያ ነው፤ ንቃትን የሚጨምር ነው፤ ረሃብ የሚያስከትለውን መነጫነጭ መከላከያ ነው፤ በዛን ወቅት ምፅዋት ለሚጠይቅ ሰው ወይም አብሮት ለሚበላ ሰው ለመመፅወት ምክንያት ነው፤ ዱዓ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ በሚታሰብበት በዚህ ወቅት ዱዓና ዚክር እንድናደርግ ምክንያት ነው፤ ከመተኛቱ በፊት ከመነየት ለተዘናጋ ሰው የጾሙን ኒያ እንዲነይት ምክንያት ነው።"
- ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ልብ ተደስቶ እንዲሰራውና የሸሪዓ ውበትን ለማሳወቅ ብያኔን ከጥበብ ጋር ማቆራኘታቸው የማስተማር ጥበባቸውን ያሳየናል።
- ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሰሑር ሰውዬው በሚበላው ወይም በሚጠጣው ትንሽ ነገርም ይገኛል።»